Sunday, October 14, 2012

የኛ ኃይል







“ፒያሳ፤ መሐሙድጋ ጠብቂኝ” በመሐመድ ሰልማን የተጻፈ እና ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈ ኢ-ልቦለዳዊ መጣጥፎች ስብስብ ነው፡፡ የዛሬ ዓመት ገደማ ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ በተባለ መንግስታዊ ባልሆነ ድርጅት  አማካይነትመጽሐፉን የመገምገሚያ ዝግጅት አምስት ኪሎ በሚገኘው ብሔራዊ ሙዚዬም ቀርቦ ነበር፡፡ በውይይቱ መሐል የመጽሐፉ ዝነኝነት ምንጮች ምን ምን ናቸው የሚል ውይይት የነበረ ሲሆን ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ‹‹ደራሲው የአዲስ ነገር ጋዜጣ ጸሐፊ የነበረ›› መሆኑን እና ‹‹ጽሑፎቹም በአዲስ ነገር ጋዜጣ እና ድረገጽ ላይ ወጥተው የነበሩ›› መሆናቸውን ጠቀሰ፡፡ ውይይቱ የአዲስ ነገር ጋዜጣ መታሰቢያ ይመስል፣ የትዝታ ጫወታው ተጧጧፈ እናም ከውይይቱ ተሳታፊዎች አንዱ የሚከተለውን ሲናገር ረዥም ጭብጨባ አዳራሹን አደመቀው ወጣቱ አስተያየት ሰጪ በንግግሩ መሃል የተጠቀመው እና ጢም ብሎ የሞላውን አዳራሽ በጭብጨባ ያናጋው ንግግር የሚከተለው ነበር፡፡

‹‹ይህ ትውልድ በአዲስ ነገር ጋዜጣ የሚደራደር ትውልድ አይደለም፡፡››

ጉዳዩን አስገራሚ የሚደርገው ወጣቱ ይህንን የተናገረው አዲስ ነገር ጋዜጣ መታተም ካቆመች ከሁለት ዓመታት በኋላ መሆኑ ሲሆን፣ አጋጣሚው የጋዜጣዋ መንፈስ በበርካቶች ልብ ውስጥ በትኩስነት መኖሩን የሚናገር ነበር፡፡

ዛሬ፣ ጥቅምት 5/2005 የዓለም የጡመራ የተግባር ቀን (Blog Action Day 2012) “የኛ ኃይል” በሚል መሪ ቃል ይከበራል፡፡ የጡመራ የተግባር ቀን በየዓመቱ የሚከበር፣ በዓለም ዙሪያ ያሉ ጦማሪዎች በሙሉ በአንድ ሐሳብ ዙሪያ የሚጽፉበት ቀን ነው፡፡ የተጀመረው እ.ኤ.አ. በ2007 ሲሆን በተመሳሳይ  ዓመት ‹‹አካባቢ››፣ በ2008 ‹‹ድህነት››፣ በ2009 ‹‹አየር ለውጥ››፣ በ2010 ‹‹ውሃ››፣ በ2011 ‹‹ምግብ›› በሚል ሲካሄድ ዘንድሮ ደግሞ በ2012 ‹‹የእኛ ኃይል›› በሚል እየተካሄደ ይገኛል፡፡

የዘንድሮው መሪ ቃል፣ ማኅበረሰብ፣ እኩልነት፣ ፀረ-ሙስና እና ነጻነትን በተመለከተ የኛ ኃይል ምን እንደሆነ በመስበክ እንዲከበር ታስቦ የተመረጠ ነው፡፡ አከባበሩ ቀላል ነው፤ አስተባባሪዎቹ እንዳስቀመጡት ‹‹profile someone or a group who inspires you by the way they made a positive influence… (ባመጡት አዎንታዊ ተጽዕኖ ያነቃቃችሁን የሆነ ሰው ወይም ቡድን በመምረጥ ጻፉ…)›› የሚል ነው፡፡

እኛም ጮክ ብለን ስናስብበት እና በጭንቅላታችን ያቃጨለችው አዲስ ነገር ጋዜጣ ብቻ ሆነች፡፡ አዲስ ነገር ጋዜጣ ለሁለት ዓመታት (ከጥቅምት 2000 እስከ ታሕሳስ 2002) ብቻ በስርጭት የቆየች ነገር ግን መራኄ አዘጋጇ መስፍን ነጋሽ የጋዜጣዋን ሁለተኛ ዓመት አስመልክቶ እንደገለፀው ‹‹አጭር ግን ረዥም ዓመት›› የኖረች ያክል የማትረሳ ጋዜጣ ናት፡፡

አዲስ ነገር ጋዜጣ በሌጣ ግለሰብ ተፅዕኖ እና ባለቤትነት የማትመራ፣ በስድስት መሥራች አባላት የተቋቋመች እና በሕፀፅ አታች (critical analysis) ጽሁፎቿ ከፍተኛ ተወዳጅነትን እና ተነባቢነትን ለማትረፍ የበቃች፣ የአንባቢውን ቁጥር ያሳደገች፣ የጸሐፍትን ችሎታ የፈተነች (standard ያኖረች)፣ በየጊዜው በማደግ እና ተፅዕኖ በመፍጠር ላይ የነበረች ጋዜጣ ነበረች፡፡ ጋዜጣዋ በቅንጅት መፍረክረክ ሰሞን ተመስርታ በተለይም ኢሕአዴግን በሚነቅፈው ማኅበረሰብ ውስጥ የነበረው የስሜት ስብራት በመጠገን ከፍተኛ መነቃቃትን ለመፍጠር የቻለች እና በማንኛውም መለኪያ አማራጭ መገናኛ ብዙሐን የሚለውን ማዕረግ ለመቀበል የምትመጥን ናት ለማለት ያስደፍራል፡፡፡

ሃሌሉያ እና Terje S Skjerda የተባሉ የጥናት ባለሞያዎች በግል ጋዜጦች ብቃት ላይ እ.ኤ.አ. በ2009 ባደረጉት እና ሁሉንም የግል ጋዜጦች ሊባል በሚችል መልኩ በነቀፉበት ጥናታቸው ውስጥ አዲስ ነገር ጋዜጣን እንዲህ ሲሉ ነበር የጠቀሷት፡-

[To be fair,…] There are newspapers which have steered away from extremist reporting and instead try to give space for different voices. Late 2007 saw the launch of Addis Neger, a private newspaper which by 2009 has grown to become one of the two largest Amharic weeklies with a weekly circulation of 25,000-30,000 copies. Its profile is serious,balanced and critical journalism with emphasis on commentaries and in-depth stories. Within the professional limitations that exist, Addis Neger and other publications have produced valuable reporting which has challenged the government in the public sphere.

([ሚዛናዊ ለመሆን…] ከፅንፈኛ ሪፖርቶች አፈንግጠው ለተለያዩ ድምፆች ቦታ የሰጡም ጋዜጦች ነበሩ፡፡ በ2002 ከአገሪቱ ሁለት ከፍተኛ ስርጭት ያላቸው (ከ25,000-30,000 ቅጂ) ጋዜጦች መካከል አንዱ ለመሆን የበቃው የአዲስ ነገር ጋዜጣ መመስረት በ2000 አጥቢያ ታየ፡፡ ይዘቱ በአስተያየቶች እና ጥልቅ ታሪኮች ላይ ያተኮረ፣ ቁምነገር አዘል፣ ሚዛናዊ እና ሂስ አዘል ጋዜጠኝነትን የተከተለ ነበር፡፡ በነባራዊው የሙያተኞች እጥረት አዲስ ነገር እና ሌሎችም መንግስትን በሕዝባዊ ክበብ ውስጥ የሚገዳደር እሴት ፈጥረዋል፡፡)

አዲስ ነገር ጋዜጣ፣ መስራቾቿ እና ጋዜጠኞቿ በመሰደዳቸው አሁን መታተም ካቆመች ሦስት ዓመታት እየተጠጋት ነው፡፡ ሁለቱ ጋዜጠኞቿ ዐብይ ተክለማርያም እና መስፍን ነጋሽም በቅርቡ ሽብርተኝነትን በመተባበር የ8 ዓመት እስር ተፈርዶባቸው በስደት ላይ ይገኛሉ፡፡ አዲስ ነገር ጋዜጣ ላይ ይወጡ የነበሩት ጽሑፎች ግን እስካሁንም ተፅዕኗቸው አልበረደም፡፡ ዳንኤል ክብረት፣በእውቀቱ ስዩም እና መሐመድ ሰልማን የአዲስ ነገር ላይ ጽሑፋቸውን መጽሐፍ አድርገዋቸው እንደአዲስ በብዙ ሺህ ኮፒዎች ተሸጠዋል፡፡ እነሠርጸ ፍሬስብሓት በሙዚቃ ላይ፣ እነማስረሻ ማሞ በፊልም ላይ የሚጽፏቸው ሂሶች የአልበሙን እና የፊልሙን ገበያ ከመወሰንም በላይ፣ ባለሙያዎቹ ለሥራቸው እንዲጠነቀቁ፣ ለአድማጭ ተደራሹም እንዲመርጥ የሚያደርጉ ነበሩ፡፡ ዶ/ር ብርሃኔ ረዳኢ በአስቂኝ የአጻጻፍ ስልቱ የሚያቀርባቸው የሕክምና ነክ ጉዳዮች የብዙዎችን ቀልብ እንደገዙ እስከዛሬም ይታወሳሉ፡፡

የአዲስ ነገር በኢትዮጵያ ፕሬስ ላይ የፈጠረችው ተጽእኖ በቀላሉ የሚታይ አልነበረም፡፡ እንደ አማራጭ፣ ተወዳጅ እና ተመራጭ ሚዲያ ሆኖ ከመቆየትም፣ በተጨማሪ የንባብ ባሕልን ወደ ፋሽንነት ለማምጣት እንዲሁም የወጣቱን ትውልድ ድምጽ የማሰማትም ሚና ነበራት፡፡ አዲስ ነገር ወደ ንባብ እና ወደ ቁም ነገር ያመጣቻቸው አያሌ ወጣቶች ዛሬም ከአዲስ ነገር አለመኖር በኋላም ሐሳብን በነጻነት ስለ መግለጽ ሲጨነቁ እና ሲጠበቡ ይታያሉ፡፡ በአዲስ ነገር መነሳሳት የተነሳም ወደ ጡመራ እና ውይይት የመጡ፣ ተስፋ ማድረግ የጀመሩም ቀላል አይደሉም፡፡

ከሚዲያው የሚመነጭ ጤናማ የአደባባይ ተዋስኦ በጠፋበት በፕሬሱ የጨለማ ዘመን ማግስት አዲስ ነገርን ማግኘት ለጤናማ ሕዝባዊ ውይይቶች መከፈት አስተዋጽዖ የነበረው ከመሆኑም በላይ ጋዜጣዋ መንግስትን በጠንካራ መልኩ በመተቸት ብትታማም የገዥውን ፓርቲ አቋም የሚያንጸባርቁ ቋሚ አምደኞች ነበሯት፡፡ አሁን በሥራ ላይ የሚገኙ እና ታዋቂ የሆኑ የሚዲያ ተቋማትም ቢሆኑ ራሳቸውን ሲገልጹ አዲስ ነገርን ማነጻጸሪያ ሲያደርጓት ተስተውሏል፡፡

በኢትዮጵያ የፕሬስ /ሐሳብን በነጻ የመግለጽ/ ነጻነት እያሽቆለቆለ ለመምጣቱ የአዲስ ነገር ጋዜጠኞችን እንኳን የሚያሠራ ክበብ አለመፈጠሩ ዐብይ ምስክር ነው፡፡ ዛሬ በዓለም የጡመራ ተግባር ቀን ጋዜጣዋን እና ጋዜጠኞቹን ማስታወስ ያስፈለገንም ለዚሁ ነው፡፡ ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት፣ የሕዝብ ድምጽ /የሕዝብን ብሶት/ የሚያስተጋባ፣ የሕዝብን መንፈስ የሚያነቃቃ ጋዜጣ ያስፈልገናል፡፡ አዲስ ነገር ጋዜጣ የፈጠረችው እና ለመግደል የሚያስቸግር መንፈስ ቢኖር ይኸው መንፈስ ነው፡፡ ዓመታት አልፈውም “ዛሬም በአዲስ ነገር የማይደራደር ትውልድ” ለመፍጠር በቅታለችና!!!

3 comments:

  1. I fully agree with the choice! The advent of Addis Neger in Ethiopian free press history ushered the threshold of a new era, shade light on the untapped potential the new generation have, gave a brim of hope that we deserve and can do better, created a vibe and a spirit that talking about politics is no longer a taboo, inspired the generation to be critical, aware and informed, motivates the generation to wake up and engage and excel in everything that we do, encourages the generation to crave for freedom, justice, equality and truth. Simply Put Addis Neger was a Fashion that the new generation was so eager to belong to.This was a huge achievement made possible by a small but vibrant team. My respect and admiration to them! Their only mistake was they went against the government that abhors the presence of a thinking animal and the advent of a critical mass that starts to question and demand, as their survival is based on the creation of the opposite!

    ReplyDelete
  2. Before two or three days, i was having a conversation with a friend.it was generally about Zone nine. We have stressed on the high potential of Zone niners to emerge as a standardized NP in the printing media& the lingering impact of AN on most of the tomaris here. The coincidence is amazing and i fully share your choice. AN was just superb! One of the great blow the big brother led govt committed on freedom of expersion is closing that highly regarded news paper. You guys are on the same energy and approach. You have more than the ones in the market ....menamen....menamen...becha bertu/tomeru...be certain also that there are lots of ppl like me &my friend who follows closely and appreciate your ideas ....

    ReplyDelete
  3. I cant agree more with the writers on how influential AN was in the Ethiopian print media. For me the most important aspect of AN's influence was that it came at a time when desperation following the 2005 election gripped the nation and people had very little idea of what could be done to resurrect the popular struggle spirit observed before the election. Not only the AN editors managed to revive that spirit and show that where there is a will there is a way but they have also demonstrated that the new generation is capable of critical and rational thinking that was so required at the time. As the writers said it is very sad that the government does not have a room even for such a civilized, rational debate and persecuted the editors to the point of exile. I am, however, hopeful when I see blogs like zone 9 that all is not lost yet and we still have a chance of making a brighter future out of the current grim reality. Keep on writing.

    ReplyDelete